ግብፅ ለኤርትራ የመሠረተ ልማት ግንባታ ልታሰማራ ነው

Date:

የግብፅ በኤርትራ ውስጥ ለሚከናወኑ የኢንዱስትሪ እና የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች የሚውሉ የቴክኒክ ባለሙያዎችን ለማሰማራት እና ዝርዝር የአዋጭነት ጥናቶችን ለማካሄድ መዘጋጀቷን አስታወቀች።

ይህ የተነገረው የግብፅ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ካሊድ ሀሺም ከኤርትራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ጋር በካይሮ ባደረጉት ስብሰባ ወቅት ነዉ።

​ሚኒስትር ካሊድ ሀሺም እንደገለጹት፣ ግብፅ ያላትን የኢንዱስትሪ ልምድ ለኤርትራ በማካፈል በአገሪቱ ስልታዊ የሆኑ ፋብሪካዎች እና የመሠረተ ልማት አውታሮች እንዲገነቡ ድጋፍ ታደርጋለች።

በተጨማሪም ግብፅ በኤርትራ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ማዕከላትን በመገንባት የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት እና በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ እንቅፋቶች በመቅረፍ ረገድ የበኩሏን ድርሻ ለመወጣት ተስማምታለች።

ይህም በቀይ ባሕር ቀጣና ያለውን ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር አዲስ ምዕራፍ እንደሚከፍት ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...

በ’ፊንቴክ’ የማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩት ላይ ተጨማሪ ቀጠሮ ተሰጠ

በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ስም በተፈጸመ  የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር...

የጣሊያን ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያደረጉት የኢንቨስመንት መጠን 723 ሚሊዮን ዩሮ መድረሱ ተሰማ

ከ20 በላይ የጣሊያን ኩባንያዎች  በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን...

የቴሌግራም ማስጠንቀቂያ

ቴሌግራም (Telegram) ኦፊሴላዊ ያልሆኑ የቴሌግራም መተግበሪያዎችን (Unofficial Apps) በሚጠቀሙ...