ቴሌ ብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ ኤክስፖ 2017

Date:

«ቴሌብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ ኤክስፖ 2017» በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ከመጋቢት 19 ቀን እስከ ሚያዝያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም ይካሄዳል።

ታሜሶል ኮሙዩኒኬሽን በዛሬው እለት በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጸው፥ ይህ ኤክስፖ ከዚህ ቀደም ከተደረጉ የንግድ ትርኢቶች የተለየ እና ልዩ የሚያደርጉት በርካታ ዝግጅቶች ማቀዱን ገልጿል።

በዚህ ኤክስፖ ጎብኚዎች የተለያዩ የፆም ምግቦች (በብፌ መልክ) በአንድ ቦታ በ150 ብር ከነፃ የስንቅ ማልት ጋር ያገኛሉ።

ከኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ የሆነውን የ50 ሚሊዮን ብር ሎተሪ በኤክስፖ ላይ በልዩ ሁኔታ ይተዋወቃል።

2.8 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የኤሌክትሪክ መኪና እና የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል እንዲሁም አይቴል የሞባይል ቀፎ ለሽልማት ቀርቧል።

ከመደበኛው የንግድ ትርኢት ባለፈ የባህል፣ የትምህርት እና የመዝናኛ መድረክ የቀረበ ሲሆን የሀገራችንን ባህል እና እሴቶች የሚያንጸባርቁ ልዩ ልዩ መርሃ ግብሮች ይኖሩታል።

ታሜሶል ኮሙዩኒኬሽን ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሉሽን እና ከሊያን ቢዝነስ ግሩኘ ጋር በመሆን አዘጋጅተውታል፡፡ ሀገሬ ቴቪ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...