በቀነኒ አዱኛ ሞት ዙሪያ ፖሊስ የምርመራ ውጤቶች አሁንም አልደረሱኝም አለ

Date:

በፍቅር አጋሩ ቀነኒ አዱኛ ግድያ ተጠርጥሮ በእስር ላይ የሚገኘው ድምጻዊ አንዱአለም ጎሳ በዛሬው ዕለት በአራዳ ምድብ ችሎት ለሦስተኛ ጊዜ የቀረበ ሲሆን፤ ፖሊስ በችሎቱ “የፌደራል ፖሊስ ፎረንሲክ የምርመራ ውጤቶቹ አሁንም አልደረሱኝም” በማለት 14 ቀን ተጨማሪ ቀናት ጠይቋል።

በዛሬው ዕለት በችሎቱ የፖሊስ የምርመራ ውጤት ይጠበቅ የነበረ ቢሆንም ፖሊስ የ15 ሰዎች መረጃ ማሰባሰቡን በመግለጽ፤ ነገር ግን ፎረንሲክ የምርመራ ውጤቶቹ ስላልደረሱት ተጨማሪ ቀናትን ጠይቋል።

የአንዱዓለም ጠበቃ በበኩሉ የቀነኒ ዲያሪ እሱ ጋር እንዳለ ጠቅሶ፤ ቀነኒ ሯሷን ለማጥፋት በተደጋጋሚ መድኃኒት ወስዳ እንደነበር ተፅፎ ማግኘቱን አስታውቋል።

“ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ መፈቀድ የለበትም! አንዱዓለም የዋስ መብቱ ሊጠበቅለት ይገባል” ብሎ ተከራክሯል።

በተጨማሪም “ከእስር ወጥቶ የሙዚቃ ስራውን ለፋሲካ ያቅርብ የሚለው የዩቲዩብ ዘገባ የተሳሳተ ነው ሊታረም ይገባል” ብሏል።

ፍርድ ቤት የሁለቱን ክርክር በመስማት የክርክሩን ውሳኔ ለመስጠት ለነገ ማክሰኞ ጠዋት ቀጥሮ ሰጥቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...