አሜሪካ በኤርትራ የሚገኘውን ጨምሮ 10 ኤምባሲዎቿን ልትዘጋ ነው

Date:

  • ከሚዘጉት ኤምባሲዎች 6ቱ በአፍሪካ የሚገኙ ናቸው ተብሏል

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት በኤርትራና ደቡብ ሱዳን የሚገኙትን ጨምሮ 10 ኤምባሲዎቹን ለመዝጋት ማቀዱ ተገለጸ።

ከኤምባሲዎቹ በተጨማሪ 17 ቆንስላዎቹንም ለመዝጋት ማቀዱን ኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ዘግቧል።

የውጭ ጉዳይ መ/ቤቱ እንዲዘጉ ባቀዳቸው ኤምባሲዎች ይከናወኑ የነበሩ ስራዎችን በአጎራባች ሀገራት ኤምባሲዎች ለማከናወን ማቀዱንም ዘገባው ጠቁሟቋል።

የኤምባሲዎቹና ቆንስላዎቹ መዘጋት የትራምፕ አስተዳደር የፌደራል መንግሥትን ባጀት ለመቀነስ እየወሰደ ያለው እርምጃ አካል ነው ተብሏል።

አሜሪካ ለመዝጋት ካቀደቻቸው አስር ኤምባሲዎች መካከል ስድስቱ በአፍሪካ የሚገኙ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

በሶማሊያ ሞቃዲሾ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲም ሙሉ በሙሉ እንዲዘጋ፣ ካልሆነ ደግሞ ሰራተኞቹ በከፍተኛ ቁጥር እንዲቀነሱ ሃሳብ መቅረቡን ዘገባው አመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...