“ባለፉት 8 ዓመታት እንደ ላሚን ያማል ዓይነት ድንቅ ተጫዋች አይቼ አላውቅም” – ሲሞን ኢንዛ

Date:

“ባለፉት 8 ወይም 9 ዓመታት እንደ ላሚን ያማል ዓይነት ድንቅ ተጫዋች አይቼ አላውቅም” ሲሉ የኢንተር ሚላን አሠልጣኝ ሲሞን ኢንዛጊ ለተጫዋቹ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።

ዛሬ ምሽት በተደረገው የሻምፒዮንስ ሊግ የግማሽ ፍፃሜ የመጀመሪያ ጨዋታ ባርሴሎና ኢንተር ሚላንን በሜዳው አስተናግዶ 3 አቻ ተለያይቷል።

በጨዋታው የባርሴሎናው አዳጊ ተጫዋች ላሚን ያማል ድንቅ ብቃቱን ያሳየ ሲሆን ጠንካራ የሚባለውን የኢንተር ሚላን የተከላካይ መስመር አታልሎ በማለፍ ለክለቡ አንድ ግብ አስቆጥሯል።

የ17 ዓመቱ ላሚን ያማል በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ታሪክ በግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ግብ ያስቆጠረ በዕድሜ ትንሹ ተጨዋች ሆኗል።

በዚህ ብቃቱ የተደነቁት የኢንተር ሚላኑ አሠልጠኛል ሲሞን ኢንዛጊ፣ “የእሱን እንቅስቃሴ ለመግባት ሁለት እና ሦስት ተጫዋችን መመደብ ነበብን” ሲሉ ከጨዋታው በኋላ ተናግረዋል።

“እንደ ላሚን ያማል ያሉ ባለድንቅ ተሰጥኦ ተጫዋቾች በየ50 ዓመቱ አንዴ የሚከሰቱ ናቸው” ሲሉም ነው አድናቆታቸውን የገለጹት።

የባርሴሎናው የአጥቂ መስመር ተጫዋች ላሚን ያማል በ17 ዓመቱ ዛሬ 100ኛ ጨዋታውን ማድረግ ችሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...