የፖርቹጋላዊው ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ ልጅ የሆነው ክርስቲያኖ ጁኒየር ለፖርቹጋል ከ15 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የመጀመሪያ ጨዋታውን በዛሬው ዕለት አድርጓል።
ክርስቲያኖ ጁኒየር የፖርቹጋል ከ15 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ከጃፓን አቻው ጋር ባደረገው ጨዋታ አባቱ የሚታወቅበትን 7 ቁጥር ማልያ በመልበስ በ53ኛው ደቂቃ ተቀይሮ ገብቷል።
የክርስቲያኖ ሮናልዶ እናት ማሪያ ዶሎሬስ ዶስ ሳንቶስ በሜዳው ተገኝተው ልክ ለልጃቸው እንደሚያደርጉት ሁሉ ለልጅ ልጃቸውም ድጋፋቸውን አሳይተዋል።
በጨዋታው የፖርቹጋል ከ15 ዓመት በታች ብሔራዊ ጃፓን 4 ለ 1 በሆነ ውጤት ያሸነፈ ሲሆን ክርስቲያኖ ጁኒየር ግብ አላስቆጠረም።
