የአገልግሎቱ የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዋር አብራር እንደገለጹት ገቢው ከኢነርጂ ሽያጭ፣ ከአዲስ ደንበኞች መስተንግዶ፣ ከማያገለግሉ ንብረቶች ሽያጭና ከሌሎች ልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች ነው የተገኘው፡፡
እንደ ኤፍ ኤም ሲ ዘገባ ባለፉት ዘጠኝ ወራትም በአጠቃላይ 43 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ 42 ቢሊየን ብር ገቢ መገኘቱን አስታውቀዋል ፡፡
ከኢነርጂ ሽያጭ ብቻ 30 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር መገኘቱን ገልጸው 356 ሺህ 935 አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም ጠቅሰዋል፡፡
