ከተማን አንድ ወጥ ቀለም መቀባት በሞያው አይመከርም

Date:

አዲስ አበባ ህንፃዎቿም፣ መኖሪያ ቤት አጥሮቿም ንግድ ቤቶቿም ተመሳሳይ ቀለም ተቀብተዋል፤ እየተቀቡም ነው፡፡

ይህም ህንፃን ከህንፃ ለመለየት እንኳን አስቸጋሪ ሲያደርገው ይታያል። አሰራሩ ወደ ሌሎች ከተሞችም እየተዛመተ ነው፡፡

ይህንን የቀለም ቅብ ጉዳይ እንዴት ይታያል ስንል የዘርፉ ባለሞያን ጠይቀናል፡፡

ኢንጂነር ጌታሁን ሄራሞ የቀለም ቅብ ሳይንስ ባለሞያ ናቸው። እሳቸውም ከሌሎች ያደጉ ሃገራት ልምድ አንፃር ከተማን አንድ ወጥ ቀለም መቀባት በሞያው አይመከርም ይላሉ።

ባለሞያው በተለየ ምክንያት ከፍተኛ የፀሐይ ሙቀትና በረሃማ የአየር ንብረት ውስጥ ያሉ ከተሞችን የሙቀት መጠን ለመቀነስ ካልሆነ በቀር እንደ አዲስ አበባ ያሉ ከተሞችን ተመሳሳይ ቀለም ማልበስ #ቀለም ከማህበረሰብ ጋር ያለውን የታሪክ፣ የስነ ልቦና እና የፍልስፍና መስተጋብር ሳይንሳዊ ትርጉም ይጣረሳል ይላሉ።

በከተማ የቀለም ቅብ ሳይንስ (Urban color planning) ህግ ስርዓት ያልጠበቀ ዥንጉርጉር የከተማ ቀለም ቅብና በተቃራኒው ደግሞ የአንድ አይነት ወጥ የቀለም ቅብ አይፈቀድም የሚሉት ኢንጅነር ጌታሁን ሄራሞ ሌሎች የክልል ከተሞች እንደ አዲስ አበባ ወጥ ቀለም ሳይሆን አከባቢያዊ የከተማ ቅብ ስርዓትን (zonal coloring system) እንዲጠቀሙ መክረዋል።

ባለሞያው አከባባያዊ የከተማ ቀለም ቅብ ስርዓት፤ በአንዲት ከተማ ውስጥ ያሉ ሰፈሮችን ታሪክ፣ የማህበረሰብ ስነልቦናና ፍልስፍና ማስረዳት ይችላል ነው የሚሉት።

ሙሉ ዘገባውን በድምጽ ያድምጡ…. https://www.mixcloud.com/ShegerFM/tgh5r/

ከሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...