ሀርቫርድ ዩኒቨርስቲ ዓለም አቀፍ ተማሪዎችን እንዳይቀበል ተከለከለ

Date:

የትራምፕ አስተዳደር ሀርቫርድ ዩኒቨርስቲ ዓለም አቀፍ ተማሪዎችን እንዳይቀበል ያገደ ሲሆን ይህም ከአሜሪካ አንጋፋው ዩኒቨርስቲ ጋር ያለውን አለመግባባት አባብሶታል።

የአገር ውስጥ ደህንነት መስርያ ቤት ኃላፊ ክሪስቲ ኖኤም በኤክስ ገጻቸው ላይ እንደጻፉት አስተዳደሩ ሀርቫርድ “ተማሪዎች እና ስደተኛ ያልሆኑ ተማሪዎችን መቀበል የሚያስችለውን ዕድል ሕግን ማክበር ባለመቻሉ ምክንያት ተሰርዟል” ብለዋል።

“ይህ በመላው አገሪቱ ለሚገኙ ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች እና የትምህርት ተቋማት እንደ ማስጠንቀቅያ ይሁናቸው” ሲሉ ሐሙስ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ልጥፍ ላይ ጽፈዋል።

ሀርቫርድ ውሳኔውን “ሕገ ወጥ” ሲል በመግለጫው አውግዞታል።

“ከ140 በላይ አገራት የመጡ እና ዩኒቨርሲቲውን እና ይህችን አገር በማይተመን መልኩ የሚያበለጽጉትን ዓለም አቀፍ ተማሪዎቻችንን እና ምሁራኖቻችንን ለማስተናገድ ሙሉ በሙሉ ቁርጠኞች ነን” ሲል ዩኒቨርሲቲው በመግለጫው ላይ ምላሽ ሰጥቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...