መንግስት ሰራተኞች ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የገንዘብ ብድር አወሳሰድ እና አመላለስ ሂደት

Date:

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለመንግስት ሰራተኞች  ያለ ምንም መነሻ ዋስትና በደመወዙ ልክ እስከ 150,000 ብር የዲጅታል ብድር አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ መመሪያ ማዘጋጀቱን ይታወሳል። 

ይህንን ገንዘብ ለመበደር የCEB Birr ተጠቃሚ መሆን የሚያስፈልግ ሲሆን፣ባንኩ ከደመወዝ ከፋይ ፋይናንስ ጋር በሚኖረውን ስምምነት መሠረት፣ ተበዳሪ አካል ባለበት ሆኖ፣በCEB Birr አማካይነት አገልግሎቱን የሚያገኝ ይሆናል።

ለዚህም የብድር አወሳሰድ እና አመላለስ ሂደት እንደሚከተለው ቀርቧል ።

👉 የግማሽ ወር ደመወዝ የሚበደር ሰው፣በአንድ ወር ውስጥ ተመላሽ የሚደረግ ሲሆን ፣ ወለድ 3% ይሰላል።

👉 የአንድ ወር ደመወዝ ሲበደሩ.. ወለድ 8% የመመለሻ ጊዜ 3 ወር፤

👉የሁለት ወር ደመወዝ ሲበደሩ..ወለድ 14% የመመለሻ ጊዜ 6 ወር፤

👉የሶስት ወር ደመወዝ ሲሆን፣ ወለድ 17% በዘጠኝ ወር፤

👉የአራት ወር ደመወዝ ለሚበደር ወለድ 20% በአንድ አመት።

ማነኛውም የመንግስት ሠራተኛ ያለምንም ማስያዣ፣በዲጂታል ሲስተም ብቻ ባለበት ሆኖ፣የብድር አገልግሎቱን ማግኘት የሚችል ሲሆን፣የደመወዝ መደበኛ ሂሳብ(account ) በስልክ ቁጥር (CEB Birr) የሚተካ ይሆናል።

ማነኛውም ተጨማሪ መረጃ የሚፈልግ ሰው  ይህንን አግልግሎት ወደ ጀመሩ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በአካል በመገኘት በቂ መረጃ እና ማብራሪያ ማግኘት እንደሚቻል ይህንን የብድር አገልግሎት ከጀመሩ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...