ሲፒጄ የኢትዮጵያ መንግሥት  ሮይተርስ ጋዜጠኞችን የሥራ ፈቃድ እንዲመለስ አሳሰበ

Date:

የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (ሲፒጄ) የኢትዮጵያ መንግስት የሦስት የሮይተርስ ጋዜጠኞችን የሥራ ፈቃድ እንዲመልሱ ጥሪ አቀረበ።

ባለፈው ሳምንት የኢትዮጵያ መንግሥት በአዲስ አበባ ለሚገኙ ሦስት የሮይተርስ ጋዜጠኞች የሥራ ፈቃድ አለማደሱ እና 39ኛውን የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤን እንዲዘግቡ የተሰጣቸውን ፈቃድ መሰረዙ ይታወሳል።

እርምጃዉ የተወሰደው የዜና ወኪሉ ኢትዮጵያ ለሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል አባላት ማሰልጠኛ ካምፕ ገንብታለች የሚል የምርመራ ዘገባ ካወጣ ከጥቂት ቀናት በኋላ ነው።

የሲፒጄ የአፍሪካ ፕሮግራም አስተባባሪ ሙቶኪ ሙሞ ድርጊቱን “በዓለም አቀፍ እና በገለልተኛ ፕሬስ ላይ እየታየ ያለ አሳሳቢ የጭቆና እና የቁጥጥር እርምጃ አካል ነው” ብለዋል፡፡

ባለሥልጣናቱ የሮይተርስን የሥራ ፈቃድ እንዲመልሱ እና ትችት የሚያቀርቡ ጋዜጠኞችን እንደ ስጋት ከመመልከት እንዲቆጠቡም አሳስበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...