በቀዶ ጥገና 3.5 ኪሎ ግራም ክብደት ያለው ስብም ወጣ

Date:

የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል በሰውነቱ ላይ አላስፈላጊ የስብ ክምችትን ወይም በህክምና ስያሜው ‘Madelung’s Disease’ የነበረበትን የ40 ዓመት ግለሰብ የቀዶ ጥገና ህክምና በተሳካ ሁኔታ ማከናወኑን ገልጿል።

የቀዶ ጥገና ህክምናውን ዶ/ር ኦብሳ ቢራቱ ሲመሩት ለማጠናቀቅ 5 ሰዓታትን ፈጅቷል።

ግለሰቡ በአንገቱ አካባቢ የተከማቸው ስብ ወደ ደረቱ ወርዶ የመተንፈሻ ችግር እንዲገጥመው አድርጎት ነበር።

ከቀዶ ጥገናው በኋላ 3.5 ኪሎ ግራም ክብደት ያለው ስብም ከሰውነቱ ወጥቷል።

ታካሚው ከቀዶ ጥገናው በኋላ በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛል።

የቀዶ ጥገናውን ያከናወኑ ሃኪሞች ቡድን

  1. ዶ/ር ኦብሳ ቢራቱ
  2. ዶ/ር ሲንቦና አራርሳ
  3. ዶ/ር ብርሃኑ ንጉሴ
    እንደዚሁም በአንኤስቴሺያ ዶ/ር ኡስማን እና ዶ/ር መኩሪያ ተሳትፈዋል።

በነርስነት አብዲ፣ ዲቤ፣ ዋቅጅራ እና ተሬሳ የተባሉ የጤና ባለሙያዎች ስለመሳተፋቸው የአምቦ ዩኒቨርስቲ ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...