በተለያዩ የአለም ክፍሎች በተደረጉ የጎዳና ላይ ውድድሮች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አሸንፈዋል

Date:

በሳምንቱ መጨረሻ በተለያዩ የአለም ክፍሎች በተካሄዱ የጎዳና ላይ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ተቀዳጅተዋል ።

በቦስተን የ5 ኪሎሜትር ውድድር አትሌት ገላ ሀምበሴ 14 ደቂቃ ከ53 ሰከንድ በመግባት በአንደኝነት አሸንፋለች ።

በውድድሩ ላይ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ፣አትሌት ፅጌ ገብረሰላማ 4ኛ ፣አትሌት ለምለም ሀይሉ 5ኛ ደረጃን ይዘው ውድድራቸውን አጠናቀዋል ።

በሻናይ ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ፈታ ዘርአይ በቀዳሚነት አሸንፋለች ።

አትሌት ፈታ 1ሰዓት ከ06 ደቂቃ ከ36 ሰከንድ በመግባት የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል
ማሸነፍ ችላለች።

በሀር ቺንዶ ማራቶን በሴቶቹ አትሌት ብዙአለም ጨቅሌ አሸንፋለች።

አትሌቷ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 2 ሰዓት ከ30ደቂቃ ከ33ሰከንድ ወስዶባታል።

ፀሐይ ገብሬ በስድስት ሰከንዶች ዘግይታ ሁለተኛ ወጥታለች።

በወንዶቹ አትሌት ሞላልኝ ፋንታሁን 2 ሰዓት ከ12 ደቂቃ ከ39 ሰከንድ ውድድሩን በማጠናቀቅ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...