ኤፍቢአይ የኢራን የመረጃ መዝባሪዎች ይጠቀሙበታል ያላቸውን አራት ድረገጾች በቁጥጥር ስር አዋለ

Date:

ኤፍቢአይ መቀመጫቸውን ኢራን አድርጎ በአሜሪካ ኩባንያዎች ላይ የሳይበር ጥቃት፣ የመረጃ ምዝበራ እና ምንተፋ የሚያካሄድ ቡድን የሚገለገልባቸውን አራት ድረ ገጾች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቀ።

የአሜሪካ የፍትህ ቢሮ በቁጥጥር ሥር የዋለው “የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ የስለላ እና የደህንነት ሚኒስቴር የሚያካሄደውን የመረጃ ብርበራ እና የድንበር ተሻጋሪ ምንተፋ እቅዶችን ለማደናቀፍ የሚደረገው ቀጣይነት ያለው ጥረት አካል ነው” ብሏል።

የፍትህ ቢሮ እንዳስታወቀው፣ የተያዙት ድረ ገጾች ጋዜጠኞችን፣ የአገዛዙን ተቃዋሚዎች እና የእስራኤልን ሕዝብ እንዲገደሉ ጥሪ ይተላለፍባቸው ነበር ብሏል።

“ኢራን አሜሪካውያንን ለማሸበር እና ተቃዋሚዎችን ዝም ለማሰኘት የሐሰት ድረ ገጾችን እና ኪቦርድ ጀርባ ልትደብቅ እንደምትችል አስባ ነበር” ሲሉ የኤፍቢአይ ዳይሬክተር ካሽ ፓቴል ተናግረዋል።

“የዘመቻቸው አራቱን ምሰሶዎች አፍርሰናል፤ አልጨረስንም” ያሉት ፓቴል “ኤፍቢአይ ከእነዚህ ፈሪ የሞት ዛቻዎች እና የሳይበር ጥቃቶች በስተጀርባ ያሉትን ሁሉመም ተዋናዮች ያድናል፤ እንዲሁም የአሜሪካን የሕግ አስከባሪ ኃይሎች ሙሉ ኃይል በእነሱ ላይ ያዘምታል” ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...