የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የ1.2 ቢሊዮን ዩሮ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

Date:

በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መካከል በሚካሄደው የንግድ ፎረም መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ፣ የአውሮፓ ህብረት ከአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ሴክሬታሪያት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ሰኞ ዕለት እንደሚፈራረም ታውቋል።

ሚያዚያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚደረገዉ ይህ ስምምነት የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን እና ስምንት አባል ሀገራት በጋራ የሚያከናውኑት የ“ቲም ዩሮፕ ኢንሼቲቭ” አካል ሲሆን፣ በአጠቃላይ 1.2 ቢሊዮን ዩሮ የሚገመት በጀት ተመድቦለታል።

ጥምረቱ እነዚህ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራትን ማለትም (ዴንማርክ፣ ጀርመን፣ አየርላንድ፣ ፈረንሳይ፣ ኔዘርላንድስ፣ ፊንላንድ፣ ፖርቹጋል እና ስዊድን) በአንድ ላይ ያሰባሰበ ነው።

በአሁኑ ወቅት ከ80 በላይ ንቁ ፕሮጀክቶችን በአባልነቱ የያዘው ይህ ኢኒሼቲቭ፣ የአውሮፓ ህብረት ለአፍሪካ ኢኮኖሚያዊ ውህደት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተመላክቷል።

የስምምነቱ ዋነኛ ዓላማ የአፍሪካን ኢኮኖሚያዊ ውህደት መደገፍ እና የአህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነትን ወደ ተግባር ለማሸጋገር የሚደረገውን ጥረት በገንዘብና በቴክኒክ ማገዝ መሆኑ ተጠቁሟል።

capital news

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...