ትምህርት ሚኒስቴር ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች የዲግሪ ሰርተፍኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ሊከናወን መሆኑን አስታውቋል።
ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እና ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላለፈው ይህ መመሪያ በተቋማት የሚሰጡ ዲግሪዎች ህትመት ወጥ በሆነ መልኩና እንዲዘጋጁና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ታስቦ መሆኑ ተገልጿል።
በመሆኑም ተቋማቱ በዲግሪ የምስክር ወረቀቱ ላይ ሊካተትላቸው የሚፈልጉትን ሎጎ እና ሌሎች መካተት አለበት የሚሉትን ጉዳዮች እንዲያካትቱ ተነግሯል።
በተጨማሪም በየተቋማቱ በዚህ ዓመት የመውጫ ፈተና ወስደው ያለፉና ለምርቃት የተዘጋጁ ተማሪዎችን ስም ዝርዝር እንዲልኩ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።
