ሩሲያ በዩክሬን ላይ ከባድ የአየር ጥቃት መፈጸሟን ተከትሎ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አቻቸው ቭላድሚር ፑቲንን “እብድ” ሲሉ ዘለፉ።
ትራምፕ “ደስተኛ እንዳልሆኑ” እና ጠንከር ባለ እና ባልተለመደ ተግሳጽ ፑቲንን “ምን ነካው? ብዙ ሰዎችን እየገደለ ነው” ብለዋል።
በኋላም ፑቲንን “ፍጹም እብድ” በማለት ወርፈዋቸዋል።
የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ሩሲያ በምትፈጽማቸው ጥቃቶች ላይ የአሜሪካ ዝምታ ፑቲንን እያበረታታ ነው ሲሉ ቀደም ብለው ተናግረው ነበር።
በሩሲያ ላይ ከበድ ያሉ ማዕቀቦችን ጨምሮ “ጠንካራ ጫና” እንዲደረግባት አሳስበዋል።
