የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የሊግ ቅርፅ ውድድር ዛሬ ምሽት ከተደረጉት መርሐ ግብሮች በኋላ ተጠናቋል።
አርሰናል ሁሉንም ስምንት የምድብ ጨዋታዎች በማሸነፍ በአንደኝነት አጠናቆ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅሏል።
የአምናው የሻምፒዮንስ ሊጉ አሸናፊ ፒኤስጂ ስምንት ውስጥ ማጠናቀቅ ሳይችል ቀርቷል።
ሪያል ማድሪድ በበኩሉ በቤኔፊካ መሸነፉን ተከትሎ ስምንት ውስጥ ማጠናቀቅ አልቻለም።
1️⃣ አርሰናል
2️⃣ ባየር ሙኒክ
3️⃣ ሊቨርፑል
4️⃣ ቶተንሀም
5️⃣ ባርሴሎና
6️⃣ ቼልሲ
7️⃣ ስፖርቲንግ ሊዝበን እና
8️⃣ ማንችስተር ሲቲ ከአንድ እስከ ስምንት ያለውን ደረጃ በመያዝ በቀጥታ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅለዋል።
ከ 9 – 24 ያለውን ደረጃ ይዘው ያጠናቀቁ ቡድኖች በቀጣይ ጥሎ ማለፉን ለመቀላቀል አንድ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ያደርጋሉ።
ከ 25 በኋላ ያለውን ደረጃ ያጠናቀቁ ክለቦች ከአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ውጪ ሆነዋል።
tikvahethsport
