ሽሬ ከተማ የቀጠናው የህገወጥ ወርቅ ገበያ ማእከል ሆኗል

Date:

በከተማዋ ለሚገኝ የብሄራዊ ባንክ ቅርንጫፍ የሚቀርበው ወርቅ ከኮንጎ ጭምር የሚመጣ መሆኑ ነው የተገለፀው።

ብሄራዊ ባንክ ለወርቅ አቅራቢዎች ከአለም ገበያ በላት እጅግ ሳቢ ክፍያ የሚፈፅም መሆኑ የቀጠናው ወርቅ ምርት ወደ ሽሬ እየገባ ለመንግስት እንዲሸጥ ማድረጉ ነው የተጠቀሰው።

በዚህም ከኤርትራ፣ ሱዳን እንዲሁም ኮንጎ ጭምር ወርቅ ወደ ትግራይ ክልል ሽሬ ከተማ እየመጣ በአቅራቢዎች ለብሄራዊ ባንክ እንደሚሸጥ ተጠቅሷክ።

ይሁንና ከነዚህ አገራት እና በኢትዮጵያ የሚገኙ ወርቅ አምራች ክልሎች ወደ ሽሬ የሚመጣው ጥራቱ የቀነሰ ወርቅ በትግራይ ከሚመረተው ጥራቱ ከፍ ያለ ወርቅ ጋር በመደባለቅ እንደሚሸጥ ነው የሚነገረው።

ይህን ችግር ለመቅረፍ ማእከላዊ ባንኩ ጥረት መጀመሩ ነው በሪፖርተር ዘገባ የተገለፀው።

በተጠናቀቀው በጀት አመት ከወርቅ ወጪ ንግድ ከ3.4 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።
ከዚህም ውስጥ ምንጩ ከትግራይ የሆነው እጅግ ከፍተኛ ድርሻ የያዘ ነው።

ነገር ግን የክልሉ ሀላፊዎች ከትግራይ ቀረበ በተባለው ወርቅ ላይ ሁሉም በክልሉ የተመረተ ነው ወይ የሚለው ላይ ጥያቄ አላቸው።

ሃለሰፊዎቹ ከትግራይ ቀረበ የተባለው ወርቅ ከተለያዩ ክልሎች እና ጎረቤት አገራት  ጭምር ወደ ክልሉ መጥቶ የተሻለ ጥራት ካለው ምርት ጋር ተቀላቅሎ የቀረበ መሆኑን ይገምታሉ።

ትግራይ ክልል አና የኤርትራ የጦር መሪዎች በዚህ ንግድ በጥምረት እንደሚሰሩ ነው ዘገባው ያከለው።

በ2017 ለብሄራዊ ባንክ የቀረበ ወርቅ

ትግራይ -39 ቶን
ጋምቤላ-5.4 ቶን
ኦሮሚያ-5.2 ቶን
ቤንሻንጉል ጉምዝ-4.7 ቶን
ሲዳማ-165 ኪግ
ምንጭ፡ ማእድን ሚኒስቴር

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...