ታጣቂዎች ትላንት አመሻሽ ጀምሮ በከተማይቱ ተኩስ አስነስተዋል።
ታጣቂዎች በከተማይቱ ዋና ዋና አካባቢዎች ተኩስ የከፈቱት አዛዣቸው የሆኑት አብዱልጋሊ ኪኪል መገደላቸውን ተከትሎ እንደሆነ ተገልጿል።
ተኩስ የከፈተው ታጣቂ ቡድን ከአራት አመታት በፊት ከብሄራዊ አንድነት አስተዳደሩ ጋር በመስማማት ወደ ስልጣን የመጣ ነው ተብሏል
ትሪፖሊን በመቆጣጠር የሚያስተዳድረው ብሄራዊ አንድነት መንግስት፤ የትሪፖሊ ነዋሪዎች ለደህንነታቸው ሲባል በቤታቸው እንዲቆዩ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።
ሃገሪቱ የሙአመር ጋዳፊ ከተገደሉ በኋላ ምስራቅ እና ምዕራብ በሚል በሁለት አስተዳደሮች በመራት ላይ የምትገኝ መሆኗ የሚታወቅ መሆኑን ሮይተርስ አስታውሶታል።
