አሜሪካና ሳዑዲ አረቢያ የ600 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የንግድ ስምምነት 

Date:

አሜሪካና ሳዑዲ አረቢያ 600 ቢሊየን  የአሜሪካ ዶላር የሚያወጣ የንግድ ስምማነት በዛሬው ዕለት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱን ዛሬ ለይፋዊ  የስራ ጉብኝት ሳዑዲ አረቢያ የገቡት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የሳዑዲ አረቢያው አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ሳልማን ናቸው የተፈራረሙት።

ስምምነቱ ሳዑዲ አረቢያ በዓለም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ማዕከል ለመሆን ለያዘችው እቅድ አስፈላጊውን የቴክኖሎጂ ግብዓት ከአሜሪካ  የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ለማግኘት ያስችላታል።

የስምምነት ስነ-ስርዓቱን የአሜሪካ የቴክኖሎጂ አምራች ድርጅቶች  ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች በአካል ተገኝተው ታድመዋል።

ከቴክኖሎጂ ባለፈ አሜሪካ ለሳዑዲ አረቢያ የምታደርገውን የ142 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የጦር መሳሪያ ሽያጭ ስምምነቱ ያካትታል ተብሏል።

በዛሬው ዕለት ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ያቀኑት ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ በቀጣይ በወደ ኳታር እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በማቅናት በአጠቃላይ ከ1 ትሪሊዮን የአሜሪካ ዶላር  በላይ የሚሆን የንግድ ስምምነት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...