የአፍሪካ ሕብረት በቅኝ ግዛት ካሳ ዙሪያ በአውሮፓ ሕብረት ላይ ጫና ሊያሳድር ይገባል ተባለ

Date:

በአፍሪካ ሕብረት የዲያስፖራ ጉዳዮች ክፍል ኃላፊ አንጄላ ናአ አፎሌ ኦዳይ ለአውሮፓ ሕብረት በአፍሪካ ላይ ለፈጸመው ቅኝ ግዛት እና ለአትላንቲክ የባሪያ ንግድ ካሳ እንዲከፍል ጫና ሊደረግበት እንደሚገባ ተናገሩ።

ኃላፊው ለእንግሊዝ ሚዲያ በሰጡት መግለጫ በአውሮፓና በሌሎችም ቦታዎች የቀኝ ዘመም እንቅስቃሴ እየጨመረ ቢመጣም አፍሪካ ካሳ መጠየቅ አለባት ብለዋል። “የተለያዩ አመቺ ያልሆኑ ጉዳዮች ቢኖሩም የካሳ ክፍያን ለማንሳት ከዚህ የተሻለ ጊዜ የለም” ሲሉ ተደምጠዋል ።

በየካቲት ወር የተካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤም የማካካሻ ፍትሕ እና በአህጉሪቱ ላይ ለተፈፀመው ዘር ተኮር አድልዎ መፍትሔ መፈለግ ላይ ያተኮረ ነበር።

ሕብረቱ ይህን ግብ ለማሳካት ዲፕሎማሲያዊ ጫና ከመፍጠር ባለፈ በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤቶች ሕጋዊ እርምጃ መውሰድን እንደ አንድ ስትራቴጂ እንደሚመለከት ቀደም ሲል አስታውቋል።
በዚህ ረገድ ኃላፊው የአፍሪካ ሕብረት ከአውሮፓ ሕብረት እንዲሁም ከካሪቢያን አገራት ጋር የሚያደርገው ትብብር ካሳን በተመለከተ የተቀናጀ አቋም ለመፍጠር ጠቃሚ መንገድ እንደሆነ ጠቁመዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...