የኡጋንዳ አየር መንገድ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ድሪምላይነር ተከራየ

Date:

የኡጋንዳ አየር መንገድ ተቋርጦ የነበረውን የረጅም ርቀት በረራ ለማስቀጠል እንዲረዳው ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የ”Wet-lease” ኪራይ ስምምነት መፈራረሙ ተገልጿል።

በስምምነቱ መሰረት ET-ASI የተመዘገበ ቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን ከ43 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች ጋር ኢንቴቤ ገብቷል።

ይህ አስቸኳይ ውሳኔ የተላለፈው የአየር መንገዱ ሁለት ኤርባስ አውሮፕላኖች ባልታሰበ የጥገና ምክንያት ከአገልግሎት ውጪ በመሆናቸው ነው።

አየር መንገዱ ይህንን እርምጃ የወሰደው በተለይ የለንደን ጋትዊክ በረራ እንዳይቋረጥና በአቪዬሽን ህግ መሰረት ስራ በሚበዛባቸው አውሮፕላን ማረፊያዎች የተሰጠው የበረራ ሰዓት እንዳይቀማ ለመከላከል ነው።

ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ የአየር መንገዱን ክፍተት ለመሙላት የቀድሞውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ግርማ ዋቄን በአማካሪነትና በተጠባባቂ ስራ አስፈፃሚነት መመደባቸው የሚታወስ ሲሆን፣ አየር መንገዱ ለተሳፋሪዎቹ አማራጭ መፍትሄዎችን እያመቻቸ መሆኑን አስታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...