የኮሜዲያን ወንድወሰን ሥርዓተ ቀብር ተፈፅመ

Date:

የኮሜዲያን እና ደራሲ ወንድወሰን አውራሪስ ሥርዓተ ቀብር ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈፅሟል።

በድንገተኛ የልብ ሕመም ምክንያት ህዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም ሕይወቱ ያለፈው ኮሜዲያን እና ደራሲ ወንድወሰን፥ በበርካታ የኮሜዲ ሥራዎቹ፣ ፊልሞቹ፣ የመድረክ ቴአትር እና የሬዲዮ ፕሮግራም ይታወሳል።

በመተወን ብቻ ሳይሆን በድርሰትም የላቀ ተሰጥኦ እንደነበረው የሚነገርለት የጥበብ ሰው በቀብር ሥነ ስርዓቱ ላይ ቤተሰቦቹ፣ የሙያ አጋሮቹ እና አድናቂዎቹ ተገኝተዋል።

በ49 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ኮሜዲያን ወንድወሰን አውራሪስ ባለትዳር እና የአንድ ሴት ልጅ አባትም ነበር።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...