ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ በቀን እስከ 15,000 ቶን ሲሚንቶን አመረተ

Date:

ይህም  በአጭር ጊዜ ውስጥ #የሲሚንቶ_ገበያ እንዲረገጋ አድርጓል ብሏል፡፡

ፋብሪካው ባለፉት 6 ወራት ከ12 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ሲሚንቶ ወደ ገበያ ማቅረቡንም ተነግሯል፡፡

ፋብሪካውም በሙሉ አቅም ወደ ምርት ሂደት የገባው በያዝነው ዓመት መስከረም ወር ላይ እንደሆነ ይታወሳል።

ባለፉት 6 ወራት በሲሚንቶ ገበያው ላይ ከፍተኛ መረጋጋትና የዋጋ ቅናሽ ከማሳየት ባለፈም ሲሚንቶን ለማግኘት በየፋብሪካው ይኖር የነበረውን ወረፋ ሙሉ ለሙሉ አስቀርቻለሁ ብሏል።

ፋብሪካው ከኢትዮጵያ የሲሚንቶ ገበያ ውስጥ ከ38 በመቶ በላይ የሚሆነውን የሲሚንቶ አቅርቦት ሸፍኛለሁ ሲልም አስረድቷል፡፡

በአማራ ክልል በእንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ አቅራቢያ የተገነባው ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ በሚገኝበት አካባቢ የምገባ ማእከል፣ የተማሪዎች ድጋፍና የቤት ማደስ ስራዎችን እና መሰል ስራዎችን እየከወነ መሆኑንም ሰምተናል፡፡

ፋብሪካው ወደፊት ከሲሚንቶ በተጨማሪ ለአፈር ማገገም ከፍተኛ ሚና ባለው የጂብሠም ምርት ዘርፍ ለመሠማራት የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝም ተናግሯል፡፡

የሸገርን ወሬዎች፣

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...