ራይድ ትራንስፖርት ከቦስተን ፓረተነርስ ጋር ዓለም አቀፍ ይዘቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት በሚችልበት ሁኔታ በጋራ ለመስራት የስራ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
ሁለቱ ተቋማት ግዙፍ አገልገሎት አቅራቢዎች እንደመሆናቸው መጠን በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል፡፡ በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የራይድ ትራንስፖርት ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሳምራዊት ፍቅሩ ራይድ ትራስፖርት በአገራችን የዲጂታል ትራንስፖርት አገልግሎት ፈር – ቀዳጅ እንደሆነ ገልፀው፣ ሰዎችን ከዕድሎች ጋር በማገኛኘት የዕለት ተዕለት የኑሮ ዘይቤያቸው የተሻለ እንዲሆን መስራት የተመሰረተበት ራዕይ መሆኑ አስረድተዋል ፡፡
ሰለሆነም ይህንን ራዕይ ለማሳካት ከተለያ አገር-አቀፍ እና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በትብብር እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው ከቦስተን ፓርትነርስ ጋር እያደረግን ያለነው ይህንኑ ዓላማችንን የበለጠ ለማሳለጥ ነው ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የቦስተን ፓረተነርስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታዲዎስ ጌታቸው ድርጅታቸው ላለፉት 24 ዓመታት አዳዲስ የቱሪዝም አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ ሲያቀርብ የቆየ ተቋም መሆኑን ተናግረው በተለያዩ ከተሞች አገልግሎቶቹን እያሰፋ ይገኛል ብለዋል፡፡
ከራይድ ጋር በምናደርገው ስምምነትም፡-
1ኛ እንደ እንጦጦ ፓርክ፣ አፍሪካ ቪሌጅ ፣ ኩሪፍቱ ቢሾፍቱ ሪዞርቶች ራይድ የኤሌክትሪክ መኪኖችን በመመደብ ከቦስተን ፓረተነርስ ጋር በጋራ ይሰራል፣
2ኛ በኩሪፍቱ ሪዞርቶች በሚካሄዱ ትልልቅ ስብሰባዎች፣የጋብቻ ስነ-ስርዓቶች እና ኮንሰርቶች በሚዘጋጁበት ወቅት ራይድ ትራንስፖርት በቂ እና አስተማማኝ ትራንስፖርት ያቀርባል፣
3ኛ የራይድ ትራንስፖርትንም ሆነ የቦስተን ፓርትነርስን አገልግሎቶችን መልካም ስም እና ዝና በጠበቀ መልኩ የጋራ የገበያ ትስስር፣ የማስተዋወቅ እና የብራንድ ፕሮሞሽን ስራዎችን በትብብር ይሰራሉ፣
4ኛ ራይድ ትራንስፖርት አግልግሎት ለኩርፍቱ ሪዞርት ÷ ለቦስተን ስፓ ደንበኞች ያለምንም እንግልት በሚንቀሳቅሱበት የቱሪስት መስህብ ዘመናዊ ትራንስፖርት ያቀርባል፣
5ኛ አዳዲስ የገበያ ተደራሽነትን የሚያሰፉ ፓኬጆችን በጋራ በማዘጋጀት ለተጠቃዎች ለማድረስ በጋራ እንስራለን ሲሉ በስምምነቱ ላይ ተናግረዋል፡፡
