“በማይጨው ሀገረ ስብከት የነበሩ ስድስት ወረዳዎችን እራሳቸውን ችለው በሀገረ ስብከት ደረጃ እንዲተዳደሩ ተወሰነ”

Date:

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ በቅርቡ በደቡብ ትግራይ በማይጨው ሀገረ ስብከት ሲተዳደሩ የነበሩ ስድስት ወረዳዎችን “ከሃይማኖታዊ ተግባር ውጭ ፖለቲካ የሆነ ውሳኔ በመወሰን በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት እንዲተዳደሩ አድርጓል፣ ይህንንም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ሙሉ በሙሉ ይቃወመዋል” ሲል የአስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀኔራል ታደሰ ወረደ ገልጸዋል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ይህንን ያስታወቁት፣ በየዓመቱ ነሃሴ 24 ቀን ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ ይዘቱን ጠብቆ በጥንታዊቷ አክሱም ከተማ በሚከበረው “የአይንዋሪ በዓል” ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ነው።

ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ ባደረጉት ንግግር “የኦርቶዶክስ ሃይማኖትን አስቀድሞ በመቀበል ወደ መላ ሀገሪቱ ያስፋፋውን የትግራይ ህዝብ ላይ ቤተክርስቲያኗ የፈጸመችውንና ያደረገችውን በደል ታሪክ የማይረሳው ነው” ሲሉ ገልጸዋል።

ሲኖዶሱ በደቡብ ትግራይ በማይጨው ሀገረ ስብከት ሲተዳደሩ የነበሩ ስድስት ወረዳዎች በአዲስ የሀገረ ስብከት እንዲካለሉ ማድረጉን የተቹት ፕሬዝዳንቱ ታሪክ የማይረሳው ነው ሲሉ በመግለጽ የቤተክርስቲያኗ ተግባር “አሁንም {በደል መፈጸሙን} እንደቀጠለችበት የሚያሳይ ነው” ሲሉ ተችተዋል።

“የትግራይ ህዝብን ለመበተን አሁንም በቁርጠኝነት እየሰራች ለመሆኑ ማሳያ ነው” ሲሉ ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው “የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በዚህ አጋጣሚ ይህንን ተንኮል እና ሴራ በጥብቅ እንደሚቃወመው ይገልጻል” ብለዋል።

“ሁሉም የክልሉ የሀይማኖት መሪዎች እና የዕምነቶቹ ተወካዮች በጽናት እንዲታገሉት” ሲሉ ጥሪ ያቀረቡት ፕሬዝዳንቱ “በማቀውም ባለማወቅም የዚህ ተግባር መሳሪያ የሆናችሁ ወገኖች ከዚህ ተግባር ተቆጠቡ” ሲሉ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከግንቦት 6 እስከ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው ጉባኤ (አመታዊው ርክበ ካህናት) በደቡባዊ የትግራይ ዞን የሚተዳደሩ ስድስት ወረዳዎች ማለትም የአላማጣ ከተማ፣ አላማጣ፣ የኮረም ከተማ፣ ኦፍላ፣ ባታ፣ ጨርጨር እራሳቸውን ችለው ሀገረ ስብከት እንዲቋቋምላቸው ውሳኔ አሳልፏል ሲል የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጽሕፈት ቤት ግንቦት 24 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ማስታወቁ መዘገባችን ይታወሳል።

ይህንንም ተከትሎ የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጽሕፈት ቤት ግንቦት 24 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ “ሲኖዶሱ የትግራይን ግዛታዊ አንድነት በመጣስ ሀገረ ስብከት እንዲቋቋም አድርጓል ሲል በመተቸት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ ውሳኔን እንደማይቀበለው ማስታወቁን መዘገባችን ይታወሳል።

“ሀገረ ስብከት የሚቋቋመው መንግስት ዞን አደርጎ ሲያዋቅር መሆኑ እየታወቀ በጉባኤው ላይ አጀንዳ ተደርጎ እንዲያዝ በማድረግ እና ከሚመለከተው የመንግስት አካል ጋር ተነጋግረናል፣ ተረዳድተናል የሚል አሳሳች መረጃ በማቅረብ እንዲወሰን ተደርጓል” ማለቱም በዘገባው ተካቷል።

“ከህግ እና አሰራር ባፈነገጠ መልኩ ሆን ተብሎ የግዛት መስፋፋት ለማካሄድ የተቋቋመ ሀገረ ስብከት በመሆኑ የትግራይ ህዝብ እንዲቃወመው መንፈሳዊ ጥሪ እናቀርባለን” ብለዋል።

በተጨማሪም መግለጫው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን አባቶች በትግራይ በተካሄደው ጦርነት ወቅት በህዝቡ ላይ ግፍ እንዲፈጸም ተባባሪ ነበሩ ሲል ኮንኗል።
በአብነትም በወቅቱ “የባህርዳር እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ አቡነ አብርሃም ከአማራ ብልፅግና ፓርቲ አመራሮች ጋር ወደ አስመራ በማቅናት የትግራይን ህዝብ እንዴት ተባብረው ማጥፋት እንዳለባቸው ከኤርትራ መንግስት ጋር ቃል ኪዳን እንዲመሰርቱ (ቃልኪዳንእንዲገባቡ) አድርገው” ተመልሰዋል ሲል ወቀሳ ሰንዝረዋል።
አዳስ ስታንዳርድ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...