የታክሲ ሹፌሩ የ20 ሚሊዮን ብር አሸናፊ ሆኗል
በኢትዮጵያ ሎተሪ ታሪክ ከፍተኛው የ60 ሚሊዮን ብር ዲጂታል ሎተሪ ዕጣ የወጣ ሲሆን፤ በሻይ ቡና የሚተዳደሩት አቶ ብርሀኑ ጎበዜ፣ የአንደኛው ዕጣ የ60 ሚ. ብር አሸናፊ ሆነዋል፡፡
የአዲስ አበባ ኮልፌ ነዋሪ የሆነው የታክሲ አሽከርካሪ ደግሞ የሦስተኛው ዕጣ የ10 ሚሊዮን ብር አሸናፊ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሉሽን ጋር በመተባበር ያካሄደው ይህ ሎተሪ፤ ከ2 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ያሳተፈ ሲሆን አሸናፊዎቹ በ8989፣ በቴሌብር እና በድህረ-ገጽ አማካኝነት ዕድላቸውን የሞከሩ መሆናቸው ታውቋል፡፡
