የአቡ ዳቢ ፖሊስ ከ100 በላይ የተለያዩ አገራት ዜጎችን በቁጥጥር ስር አዋለ

Date:

በዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ የአቡ ዳቢ ፖሊስ የተለያዩ አገራት ዜግነት ያላቸው ከ100 በላይ ሰዎች በአገሪቱ ላይ ከሚፈጸመው ጥቃት ጋር በተያያዘ የተለያዩ ቦታዎችን “በመቅረጽ እና አሳሳች መረጃን” በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በማጋራት መያዙን አሳወቀ።

ፖሊስ በኤክስ ገጹ ላይ ባወጣው መግለጫ የተለያዩ 109 ሰዎች በሕዝቡ መካከል የተሳሳተ አመለካከትን የሚፈጥሩ እና ያልተረጋገጡ ወሬዎችን በማሠራጨት በቁጥጥር ስር አውሏል።

ፖሊስ ጨምሮም ማኅበራዊ ሚዲያን ተገቢ ላልሆነ ዓላማ የሚጠቀሙ ሰዎችን በመከታተል የአገሪቱ የደኅንነት ባለሥልጣን አስፈላጊው ሕጋዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታውቋል።

የአገሪቱ ዜጎች ወቅታዊ ሁኔታዎችን በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት እና ከሚታመኑ ምንጮች ብቻ መረጃ እንዲያገኙ በማሳሰብ የሕዝብ ጥቅምን እና አሠራሮችን በማክበር ከአንዳንድ ቦታዎች “ፎቶ ከማንሳት እና ቪዲዮ ከመቅረጽ እንዲሁም ከማጋራት እንዲቆጠቡ” አሳስቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...