ኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ ከተመሰረተ 20 አመት መሙላቱን እንዲሁም የAFFA award ምክንያት በማድረግ በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥቷል።
በአዲስ አበባ ዲሊኦፖል ሆቴል በተካሄደው ጋዜጣዊ መግለጫ የኮሌጁ የ20አመታት ጉዞ፣ የፋሽን ሾው እና የAFFA ውድድርን በተመለከተ ገለፃ አድርጓል።
በበጎ ተግባር ላይ የተመሰረተው እና ከ1500በላይ የሳኡዲ ተመላሾችን በነፃ አስተምሮ ስራ በማስቀጠር ከፍተኛ ሀላፊነት እየተወጣ ያለው ኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ በዚህ አመት ከ350በላይ ተማሪዎችን ያስመርቃል።
በተያያዘም የአፋ እጩዎች የታወቀ ሲሆን
ተሸላሚዎች
👉 1.ሳምራዊት መርስኢሀዘን – ከሳምራ ሌዘር / በኢንተርናሽናል ደረጃ የኢትዮጵያን ሌዘር በማስተዋወቅ። 2. አርቲስት ሀመልማል አባተ /ፋሽንና የባህል አልባሳትን ለረጅም ጊዜ በመልበስና በማስተዋወቅ ዲዛይነሮችን በማገዝ/
- ዮሀንስ ታጠቅ- ከጆኒ ቪዲዮ /ዲዛይነሮችና ሞዴሎችን ላለፉት 30 አመታት ፎቶ በማንሳት /
- አርቲስት መቅደስ ፀጋዬ /ፋሽንና የባህል አልባሳትን ለረጅም ጊዜ በመልበስና በማስተዋወቅ ዲዛይነሮችን በማገዝ/
- አርክቴክት ቃልኪዳን ታደሰ / ለ 15 አመታት በባህላዊ የሽመና ጨርቆች ቤትን በማስዋብ/
- ሄኖክ ሲሳይ -ከሄኒ አፍሮ / ሞዴሎችን በበጎ ፈቃደኝነት ሜካፕና ፀጉር በመስራትና ብዙ ዲዛይነሮችን በመደገፍ
- የፋሽን ዲዛይነሯ እና አርክቴክት ሜቲ ሀይለማርያም /ክርኤቲቭ ያንግ ዲዛይነር/
- ፎዚያ እንድሪስ የኢትዮዽያ የባህል አልባሳትን እለት እለት እንዲለበስ በማድረግ በመላው አለም እንዲታወቅ በማድረግ /ክርኤቲቭ ያንግ ዲዛይነር/ ናቸው።
ሽልማቱ በኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ ተዘጋጅቷል።
