“ጦቢያ” የኪነጥበብ ዝግጅት በ9 የአውሮፓ ሃገራት ትርዒቱን ሊያቀርብ እንደሆነ ተሰምቷል።
ይህም የአውሮፓ ጉዞ ጦቢያ ከሆፕ ኢንተርናሽናል ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ነው ተብሏል።ከወርሐ ሰኔ እስከ ነሐሴ ለሁለት ወራት ገደማ የሚካሄደው ዝግጅቱ የኢትዮጵያዊያንን ባህል ለማስተዋወቅ ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነም ተገልጿል።
ጦቢያ በዚህ ጉዞው በዘጠኝ የአውሮፓ ሀገራት እና በ16 የአውሮፖ ትላልቅ ከተሞች ዝግጅቱን ያቀርባል ተብሏል።
