በየዓመቱ የሚካሄደው የአዲስ ኢንተርናሽናል ፊልም ፌስቲቫል የመዝጊያ ስነ ሥርዓት ዛሬ በጣልያን ካልቸር ኢንስቲቲዮት እደሚካሄድ ተገልጿል።
የመዝጊያ አምባሳደሮች፣የፊልም ባለሞያዎች፣የ ኢንሼቲቭ አፋሪካ ዋና ዳይሬክተር አቶ ክቡር ገና እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ይካሄዳል።
ለ አራት ቀናት ሲካሄድ የቆየዉ ፌስቲቫሉ ከግንቦት 13-ግንቦት 17 ድረስ በአራት የተለያዩ ማሳያ ቦታዎች ታይቷል።
የዘንድሮው ፌስቲቫል ለየት የሚያደርገው 28 የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ነው ሲሉ የ19ኛው አዲስ ኢንተርናሽናል ፊልም ፌስቲቫል ኮርዲኔተር መና ሀይሌ ገልፀዋል።
28ቱ ፊልሞች ከ 34 በላይ ሀገሮች የተሳተፉባቸው ሲሆን የተለያዩ የጣሊያን ፊልሞች እና ስድስት የኢትዮጵያ ፊልሞች ታይተዋል።
የመዝጊያ ፕሮግራሙ በጣሊያን ካልቸር ኢንስቲቲዩት እንደሚካሄድ እና መግቢያ በ ነፃ መሆኑን የ 19ኛው አዲስ ኢንተርናሽናል በፊልም ፌስቲቫል ኮርዲኔተር የሆኑት መና ሀይሌ ለግዮን መፅሄት ገልፀዋል።
