በገሊላ ደሴት ላይ ብቸኛ የቀሩት የ107 ዓመት እናት አረፉ

Date:

በዙዋይ ደንበል ሐይቅ ገሊላ ደሴት ላይ ብቸኛ ነዋሪ የነበሩት የ107 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ እናት ወ/ሮ ኩሼ ጎንደር መሞታቸው ተገለፀ።

ገሊላ ደሴት በዝዋይ (ደምበል) ሐይቅ ላይ ከሚገኙ አምስት ደሴቶች አንዷ እና አነስተኛዋ ደሴት ናት።

የባቱ ደንበል ሀይቅ 440 ስኬዌር ኪሎ ሜትር ሥፋ ያለዉ ነዉ ፡፡ እናት ኩሼ ጎንደር ገሊላ ደሴት ላይ ለ107 ዓመት ብቻቸውን ኑሮዋቸዉን እየገፉ ነዉ።

በደሴቲቱ ከቀድሞ ጀምሮ ሰዎች ይኖሩበት የነበረ ቢሆንም ኑሮን ለመምራት ምንም አመቺ ሁኔታ ባለመኖሩ፤ ከአዛዉንቷ በቀር ሁሉም ወጥተዉ እሳቸዉ ብቻቸዉን ይኖሩ ነበር ፡፡

አዛውንቷ ‹ገሊላ ደሴት ላይ ትዳር ይዤ ስድስት ልጆችን አፍርቼበታለሁ እናም ወዴትም አልሄድም ብለው ደሴቲቱን የሙጥኝ ሲሉ ልጆቻቸው ግን ደሴቲቱን ለቀዉ›መሄዳቸዉን ተናግረዉ ነበር።

በዚህች ትንሽዬ ደሴት ላይ አንድ ገዳም ይገኛል። በገዳሙ ለአገልግሎት ከሚመላለሱ ውጪ የሚኖርበት የለም።

በዚሁ ወግ ማዕረግ ባዩበት ደሴት ስርዓተ ቀብራቸዉ ዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት ላይ ይፈጻማል ተብሏል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...