የዩጋንዳ ወታደራዊ ሄሊኮፕተር በሶማሊያ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ተከሰከሰች።
ሄሊኮፕተሯ ውስጥ ስምንት ሰዎች እንደነበሩም የሶማሊያ ዜና ምንጮች አስነብበዋል።
የአደጋው መጠን ምን ያህል ነው ስለሚለው ጉዳይም ዝርዝር ማብራሪያ እስካሁን አልወጣም።
ሄሊኮፕተሯ በሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ ኤደን አዴ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ላይ ነው የተከሰከሰችው።
ከአውሮፕላን ማረፊያው የሚወጣ ከባድ ጭስ በአካባቢው መታየቱንም የዓይን እማኞች አረጋግጠዋል፡፡
ፍንዳታ ከሰማን በኋላ በሄሊኮፕተሯ ላይ እሳት እና ጭስ ተመልክተናል በሚል የአየር መንገዱ ሰራተኛ ፋራህ አብዱሌ አሳውቋል፡፡
ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ለሄሊኮፕተሯ መከስከስ ምክንያቱ ምን እንደሆነ የታወቀ ነገር የለም፡፡
ሄሊኮፕተሯ የዩጋንዳ ጦር ሀብት ስትሆን በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር የሚንቀሳቀሰው የሰላም አስከባሪ ሀይል አካል መሆኗም ተወስቷል።
የሶማሊያ መንግስት ከአል-ቃይዳ ጋር ትስስር አለው ከሚባለው አል -ሸባብ ጋር የሚያደርገውን ውጊያ ለማገዝ የገባ ሀይል እንደሆነም ይታወቃል።
ዜናው እስከተጣናቀረበት ሰዓት ድረስ የስምንቱ ሰዎች እጣ ፈንታ ምንድን ነው የሚለውን የሶማሊያ መንግስት አላሳወቀም።
በሌላ በኩል የዩጋንዳ ጦር ሄሊኮፕተሯ የእኔ ናት ሲል ማረጋገጫ ሰቷል።
ዘገባው የቢቢሲና ሮይተርስ ነው፡፡
