በእስራኤል ታሪክ የመጀመሪያው ጥቁር ኢትዮጵያዊ ፕሮፌሰር!

Date:

ፕሮፌሰር አንበሰ ተፈራ ትውልድና ዕድገታቸው በኢትዮጵያ ሲዳማ ክልል ቦርቻ ወረዳ ነው። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በሥነልሳን (Linguistics) አግኝተዋል። በዩኒቨርስቲው በመምህርነት ሙያም አገልግለዋል።

ፕሮፌሰሩ እ.ኤ.አ በ1989 ወደ እሥራኤል ሀገር በማቅናት የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከኽብሪው ዩኒቨርስቲ አግኝተዋል፡፡ በእስራኤል ሀገር  በኽብሪውና በተል አቭቪ ዩኒቨርስቲ ከ15 ዓመታት በላይ በመምህርነት አገልግለዋል።

በዩኒቨርስቲ ቆይታቸው በዕብራይስጥ ባህልና ቋንቋ ጥናት፣ በአረብኛ፣ በአማርኛና በሲዳማ ቋንቋ ጥናት ፈር ቀዳጅ መምህርና ተመራማሪም ናቸው። ከዚህም ባሻገር በእስራኤል ትምህርት ሚኒስቴር የአማርኛ ቋንቋ ትምህርትና ጥናት አማካሪ በመሆንም ያገለገሉ ታላቅ የቋንቋ ልሂቅ ናቸው።

ፕሮፌሰር አንበሰ ተፈራ በአካዳሚክ ዓለም ቆይታቸው ከ20 በላይ የምርምር ጽሑፎችን አሳትመዋል። ሦስት መጽሐፍት ጽፈል። የሲዳምኛ ሙሉ ሥነልሳን ከዛሬ 25 ዓመት በፊት በማጥናት ለሲዳሙ አፎ እድገት ሳይንሳዊ መሠረት የጣሉ የሲዳማ ህዝብ የምንጊዜም ባለውለታ ናቸው።

እኚህ የቋንቋ (የሥነልሳን) ተመራማሪ፣ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ፣ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከተቀበሉ ከ15 ዓመታት በኋላ በማግኘት፣ በእስራኤል ሀገር ታሪክ የመጀመሪያው ጥቁር፣ የመጀመሪያው  ኢትዮጵያዊ ሆነዋል፡፡

ፕሮፌሰሩ ከበርካታ ዓመታት በኋላ ወደ  ትውልድ መንደራቸው ሲመጡ ታላቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...