ትራምፕ የጄፍሪ ኤፕስቴይን ሰነዶች ይፋ እንዲሆኑ ጠየቁ

Date:

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሪፐብሊካን ፓርቲ አባላት ታዳጊዎችን በወሲብንግድ በማሰማራት የተፈረደበት ጄፍሪ ኤፕስቴይንን ሰነዶች ይፋ እንዲያደርጉ ጠየቁ።

ፕሬዚዳንቱ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ የተወካዮች ምክር ቤት አባላት “ምንም የምንደብቀው ነገር ስለሌለ”ሰነዱን ይፋ ማድረግ አለባቸው ብለዋል።

ትራምፕ ከዚህ ቀደም  ሰነዱ እንዳይለቀቅ ሲሟገቱ የቆዩ ሲሆን፥ አሁን ላይ ምክር ቤቱ በዚህ ሳምንት በጉዳዩ ላይ ስብሰባ አካሂዳለሁ ማለቱን ተከትሎ የሰነዱን ይፋ መሆን መደገፋቸውን ቢቢሲ አስነብቧል።

በስብሰባው ምክር ቤቱ የአሜሪካ ፍትህ ሚኒስቴር የግለሰቡን ሰነዶችይፋ እንዲያደርግ አስገዳጅ ድምፅ ይሰጣል ነው የተባለው።

ታዋቂ የቢዝነስና የፖለቲካ ሰዎች ከግለሰቡ ጋር ግንኙነት አላችሁበሚል በበርካታ መገናኛ ዘዴዎች ጭምጭምታዎች ሲደመጡ ቆይተዋል።

እስካሁን ለጭምጭምታዎች በቂ ማስረጃ ያልተገኘ ሲሆን፥ በታዳጊዎችየወሲብ ንግድ የሚጠረጠረው ኤፕስቴይንም በፈረንጆቹ 2019 በማረሚያ ቤትህይወቶ አልፎ መገኘቱን ዘገባው አስታውሷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...