የሂሳብና እንግሊዘኛ ትምህርቶች በአማረኛ፣ በአፋን ኦሮሞና እንግሊዘኛ ቋንቋዎች ከዛሬ ጀምሮ በቴሌቭዥን መስጠት እንደሚጀምር ተገለጸ

Date:

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ጋር በመተባባር የሂሳብና እንግሊዘኛ ማጠናከሪያ ትምህርቶችን በአማረኛ፣ በአፋን ኦሮሞና እንግሊዘኛ ቋንቋዎች ከዛሬ የካቲት 25 ጀምሮ በቴሌቭዥን ስርጭት መስጠት መጀመሩን አስታውቋል።

የቢሮው ሀላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር)፤ ከተማ አስተዳደሩ የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ከተያዙ ስትረቴጂ ግብ ውስጥ አንዱ ትምህርት በቴሌቪዥን የማሰራጨት መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም የትምህርት ሥርጭቱ ከ4 እስከ 8ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ በመግለጽ ሥርጭቱ 13 ዘርፎች ላይ ትምህርት እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

ትምህርቱ ከየካቲት 25 ጀምሮ በኤኤምኤን ፕላስ ከሰኞ እስከ አርብ ከ11 እስከ 2 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜና እሁድ ጠዋት 2 እስከ 6 ሰዓት በሶስቱ ቋንቋዎች እንደሚሰጥም ተናግረዋል።

የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዋና ሥራ አቶ ካሳሁን ጎንፋ በበኩላቸ ስርጭቱ ኤኤምኔን ፕላስ ቻናልን ጨምሮ በትምህርት ቢሮና አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች እንደሚተላለፍ ጠቁመዋል።

ቀዳሚ ጽሑፍ
ቀጣይ ጥሑፍ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...