ትራምፕ ኢራን ያበለጸገችውን ዩራኒየም ለማስረከብ ተስማምታለች አሉ

Date:

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ያበለጸገችውን ዩራኒየም ለማስረከብ መስማማቷን ተናገሩ።

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል እየተካሄደ በነበረው የሰላም ድርድር ላይ ካላግባቡ ነጥቦች መካከል ቴህራን ያበለጸገችው ዩራኒየም አንዱ ነበር።

ፕሬዚዳንቱ በሳምንቱ መጨረሻ በዋሺንግተን እና በቴህራን መካከል ንግግር ሊቀጥል እንደሚችል ተናግረው፤ ከስምምነት ልንደርስ “በጣም ተቃርበናል” ብለዋል።

ትራምፕ በላስቬጋስ በአሜሪካ ምጣኔ ኃብት ላይ ባተኮረ ጉባዔ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ጦርነቱ “ያለምንም እንከን” እየሄደ እንደሆነ ተናግረው በቅርቡ ማብቃት አለበት ብለዋል።

ቀደም ሲል ዋይት ሐውስ ኢራን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንደማይኖራት መስማማቷን ገልጾ ነበር።

አክሎም ባለፈው ዓመት እስራኤል እና አሜሪካ የፈጸሙትን ድብደባ ተከትሎ ከመሬት በታች እንደተቀበረ የሚታመነውን የበለጸገ ዩራኒየም “የኒውክሌር አቧራ” አራግፈው ቆፍረው እንደሚያወጡ ተናግረው ነበር።

ትራምፕ በቀጣይ ዙር በሚደረገው የሁለቱ አገራት ድርድር እርግጠኛ ሆነው ታይተዋል።

ነገር ግን ከአምስት ቀናት በኋላ የሚያበቃው የተኩስ አቁም ስምምነቱ ስለመራዘሙ እርግጠኛ አለመሆናቸውን ጨምረው ተናግረዋል።

BBC

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...