የገንዘብ ድጋፍ መቀነስ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሴቶችን ለአደጋ አጋለጠ

Date:


 
ከተመድ የሴቶች ጉዳይ ድርጅት (UN Women) የወጣ አዲስ ሪፖርት እንደሚያሳየው፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተደረገው የሰብአዊ እርዳታ የገንዘብ ድጋፍ ቅነሳ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሴቶች እና ሴት ልጆች የሚያገኙትን የነፍስ አድን እርዳታ እና ጥበቃ ሙሉ በሙሉ አቋርጦታል።

ይህ የገንዘብ እጥረት በተለይም በተለያዩ ቀውሶች እና የጦርነት ቀጠናዎች ውስጥ ለሚገኙ ሴቶች የሚቀርቡ ወሳኝ ድጋፎችን ክፉኛ ጎድቷል።
 
ዓለም አቀፍ ለጋሾች የሚያደርጉትን የገንዘብ ድጋፍ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሳቸውን ተከትሎ፣ በ52 የዓለም ሀገራት ውስጥ የሚገኙ እና በሴቶች መብት ላይ የሚሰሩ ተቋማት የገንዘብ እጥረት ገጥሟቸዋል።

በዚህም ምክንያት እንደ አፍጋኒስታን፣ ሄይቲ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ባሉ አስቸጋሪ ቀጠናዎች ውስጥ የሚገኙ ሴቶች ከጾታዊ ጥቃት መከላከያ፣ ከወሊድና ጤና ክብካቤ እንዲሁም ከሌሎች የዕለት ተዕለት የሰብአዊ እርዳታዎች እየተገለሉ ይገኛሉ።
 
የተመድ ሪፖርት እንደሚያስጠነቅቀው፣ በአሁኑ ወቅት በሴቶች መብትና ደህንነት ላይ የሚሰሩ ድርጅቶች ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት የመጠለያ እና የዕርዳታ ፍላጎቶችን ማሟላት ያቃታቸው ሲሆን፣ 40 በመቶ ያህሉ ደግሞ በቀጣዩ አንድ ዓመት ውስጥ ሙሉ በሙሉ የመዘጋት አደጋ ተጋርጦባቸዋል።

ይህ አሳሳቢ ሁኔታ በአስቸኳይ መፍትሄ ካልተገኘለት፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ደካማ ሴቶች እና ህጻናት ሕይወት ይበልጥ አደጋ ላይ እንደሚወድቅ ተቋሙ አሳስቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጠቅላይ መሪ ለአባታቸው ግድያ “የበቀል እርምጃ” እንደሚወሰድ ተናገሩ

የኢራን ጠቅላይ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ በጽሑፍ ባስተላለፉት መልዕክት አባታቸው...

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የመጨረሻ ልምምዱን ሰርቷል

ቡድኑ ነገ የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር የመልስ ጨዋታውን...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር አለመጠየቋን አስታወቀች

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፤ አገራቸው...

ሱዳን ዉስጥ ለሦስት ዓመታት የተካሄደው ጦርነትን ሰለ ማቆም

የሱዳን ብሔራዊ ጦር ለሦስት ዓመታት የተካሔደውን ጦርነት ለማቆም አሜሪካ...