“የአፍሪካ ቀንድ” የተሰኘው መጽሐፍ በመጪው አርብ ገበያ ላይ ይውላል ተብሏል።
በታዋቂው የአፍሪካ ቀንድ እና የኢትዮጵያ ጉዳይ ተመራማሪ በሆኑት ፕሮፌሰር ክርስቶፈር ክላፋም ተጽፎ፣ በጋዜጠኛ ኅይለመስቀል በሸዋምየለህ ወደ አማርኛ የተመለሰው ይኽ መጽሐፍ፣ በ231 ገጾች ተቀንብቦ በ450 ብር እንደሚሸጥ ሰምተናል።
መጽሐፉ፣ ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያ እና ኤርትራ ባሏቸው ፖለቲካዊ ግንኙነቶች ላይ አተኩሮ፣ የመጪውን የቀንዱን ዕጣ ፈንታም ይዳስሳል ተብሏል።
መጽሐፉ በኹሉም የጃፋር መጽሐፍት ቤቶች እንደሚገኝም ተነግሯል።
