በኢትዮጵያ የኢንሹራንስ አገልግሎት ተደራሽነት እጅግ ዝቅተኛ መሆኑ ተገለጸ

Date:

በኢትዮጵያ የሚገኙ የኢንሹራንስ ኩባንያዎች አገልግሎት እየሰጡ ያሉት ለሀገሪቱ ህዝብ 3 በመቶ ለሚሆነው ብቻ መሆኑ ተገለጸ። ይህ ደግሞ በቂና ፍትሃዊ የሆነ የመድን ሽፋን እየተሰጠ አለመሆኑን ያሳያል።

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ 18 የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ሲኖሩ፣ ከእነዚህ ውስጥ 13ቱ ብቻ የህይወት መድን አገልግሎት ይሰጣሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በ2013 ዓ.ም. ባካሄደው ጥናት፣ ከኢንሹራንስ ኩባንያዎቹ 55 በመቶ የሚሆኑት ቅርንጫፎቻቸው በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ እንደሚገኙ አመላክቷል።

የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጀነራል ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽመልስ ገድለጊዮርጊስ እንደተናገሩት፣ ይህ የተደራሽነት ውስንነት ፍትሃዊ የመድን ሽፋን እንዳይኖር አድርጓል።

ብስራት እንደዘገበዉ አንድ በዓለም ባንክ እና በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ትብብር የተሰራ ጥናት እንደሚያሳየው፣ ኢትዮጵያውያን የህይወት መድን የማይገዙበት ትልቁ ምክንያት የግንዛቤ እጥረት ነው። የኢንሹራንስ ኩባንያዎችና ቅርንጫፎቻቸው በአቅራቢያ አለመገኘትም ሌላኛው ምክንያት መሆኑ ተጠቁሟል።

የቅዳሜ ገበያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...