የእስራኤል የጤና ሚኒስቴር ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በነበረው ውጥረት 191 እስራኤላውያን ቆስለው ወደ ሆስፒታሎች መግባታቸውን ይፋ አድርጓል።
ከተጎዱት መካከል ወታደሮችና ሲቪሎች የሚገኙበት ሲሆን፣ የአንዳንዶቹ ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑ ተገልጿል። ጦርነቱ ከተቀሰቀሰ አንስቶ እስካሁን 2,339 ሰዎች የሕክምና ዕርዳታ ማግኘታቸውን ዘ ታይምስ ኦፍ እስራኤል ዘግቧል።
በሌላ በኩል፣ ግጭቱ እየተባባሰ መምጣቱን ተከትሎ በቤሩት የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በሊባኖስ ለሚገኙ ዜጎቹ አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል።
ዜጎቹ የምግብ፣ የውሃና የመድኃኒት አቅርቦት በማዘጋጀት አስተማማኝ መጠለያ ውስጥ እንዲቆዩ አሳስቧል።
በሊባኖስ በኩል ደግሞ በእስራኤልና በሂዝቦላ መካከል እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውንና የሟቾች ቁጥር ቢያንስ 486 መድረሱን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።
