ቻይና አዲስ ሳተላይት ወደ ህዋ ያመጠቀች ሲሆን ሳተላይቷ ወደ ታቀደው ምህዋር በተሳካ ሁኔታ መድረሷ ተነግሯል።
ሺጂያን-28 ሳተላይት የጠፈር አካባቢን ለመከታተል ጥቅም ላይ እንደምትውል ተዘግቧል።
ሳተላይቷ በተሻሻለው የሎንግ ማርች-7 ተሸካሚ ሮኬት እሁድ ዕለት እንድትወነጨፍ መደረጉም ተገልጿል።
የቻይናው “ሎንግ ማርች” ሮኬት 611ኛውን ተልዕኮውን ነው በተሳካ ሁኔታ ያከናወነው።
ቀደም ሲል እ.ኤ.አ ኅዳር 19 ቻይና ተዛማጅ ለጠፈር አካባቢ ጥናቶችና ለቴክኖሎጂ ሙከራዎች ሦስት ሳተላይቶችን ሺጂያን-30A፣ 30B እና 30C ማምጠቋ ይታወሳል።
