የጉምሩክ ኮሚሽን ኢትዮጵያ ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ውህደት ሚናዋን እንድትወጣ የበኩሉን ጥረት እያደረገ እንደሆነ ገለፀ

Date:



ይህ የተገለጸው ኢትዮጵያ እና ኬንያ የአንድ አለቅ የድንበር ጣቢያዎችን ለማስፋፋት የሚያስችል ውይይት ባካሄዱበት ወቅት ነው፡፡ ውይይቱ በጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ፣ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ አሪና፣ የዓለም ባንክ የምስራቅ አፍሪካ ተወካዮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መካከል እንደተደረገ የኢትዮጵያ ጉሙሩክ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ከዓመታት በፊት አገልግሎት መስጠት የጀመረው የሞያሌ አንድ አለቅ የድንበር አገልግሎት ማዕከል ተደጋጋሚ ፍተሻዎችን በማስቀረት የተፋጠነ የጉምሩክ አገልግሎት እንዲኖር ማስቻሉን አንስተዋል፡፡

አክለውም ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ኢኮኖሚያዊ ውህደት ግንባር ቀደም ሚናዋን እንድትወጣ ኮሚሽኑ የበኩሉን ጥረት እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ እና ኬንያ ተጨማሪ የጋራ አንድ አለቅ የድንበር አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎችን ሱፍቱ እና ራሙ በሚባሉ የድንበር አካባቢዎች ለመገንባት ስለሚቻልበት ሁኔታም መክረዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...