በኮሚኒቲ ሺልድ ዋንጫ ክርስታል ፓላስ ሊቨርፑልን በመለያ ምት አሸንፏል፡፡ በዌይምብሌ በተደረገው ጨዋታ ሁለቱ ቡድኖች መደበኛ 90 ደቂቃውን ሁለት አቻ አጠናቀዋል፡፡
የሊቨርፑልን ሁለት ግቦች አዲስ ፈራሚዎቹ ሁጎ ኢኪቲኬ እና ጀርሚ ፍር,ሪምፖንግ አስቆጥረዋል፡፡ ጃን ፍሊፕ ማቴታ በፍጹም ቅጣት ምት እና ኢስማኤል ሳር በጨዋታ የክርስታል ፓስን ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው፡፡
አሸናፊውን ለመለየት በተሰጠው መለያ ምት ክርስታል ፓላስ 3 ለ 2 አሸንፏል፡፡ ሙሀመድ ሳላ እና አሌክሲስ ማክ አሊስተር የሊቨርፑልን ሁለት ተከታታይ መለያ ምትቾች መጠቀም አልቻሉም፡፡
አሰልጣኘ አርን ስሎት በዌይምብሌ ባደረጓቸው ሁለት የፍጻሜ ጨዋታዎች በሁለቱም ለመሸነፍ ተገደዋል፡፡ አሰልጣኝ ኦሊቨር ግላስነር በፓለስ ቤት 2ኛ ዋንጫቸውን አንስተዋል፡፡
